ባንኩ ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀንንአ ከበረ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን /March 8/ የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ.ም በባንኩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ያከበሩ ሲሆን፤ የባንኩን ፕሬዚዳንት ጨምሮ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እና የባንኩ ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡

በሥነ ስርዓቱ የባንኩ መሰረታዊ ሰራተኞች ማህበር የሴቶች ተወካይ ወ/ሮ ኦሪት አበበ በባንኩ ውስጥ ሴቶች ያላቸው የአመራርነት ድርሻ አነስተኛ በመሆኑ ለወደፊቱ ሴቶችን የማብቃትና ወደ ኃላፊነት የማምጣት ተግባር ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ተግባር መሆኑን አንስተዋል፡፡

የባንኩ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ አያሌው /ፒ.ኤች.ዲ/ በበኩላቸው በባንኩ ውስጥ የሴቶች ቁጥር በአመራር ቦታ አነስተኛ መሆኑን እና በባንኩ ውስጥ እየተከናወነ ባለው የሪፎርም ስራ ላይ በአንጽዖት እንደሚታይ ቃል ገብተዋል፡፡

በመጨረሻም የባንኩን ሴቶች በመወከል ንግግር ያደረጉት ወ/ሮ አልማዝ ጥላሁን እንዳሉት የሴቶች ቀን ሲከበር የበዓሉን ማክበር ብቻ ሳይሆን ሴቶች ላይ የሚደርሱ አሉታዊ ተጽዕኖዎችና ጥቃቶችን በመከላከል ሴቶችን ለተሻለ ውጤት በማብቃት ጭምር መሆን እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡