አርቲስት መቅደስ ፀጋዬ የባንኩ አምባሳደር ሆኖ እንድትሰራ የፊርማ ሥነ ሥርዓት ተካሄደ

አርቲስት መቅደስ ፀጋዬ ከመጋቢት 06 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ የባንኩ አምባሳደር ሆና እንድትሰራ የፊርማ ሥነ ሥርዓት በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት ተካሄደ፡፡   

   ባንኩ ተግባራዊ ማድረግ የጀመረውን የለውጥ ስራዎች ለደንበኞች፣ ባለድርሻ አካላት፣ መንግስትና ለህብረተሰቡ በተገቢው መንገድ ለማስተዋወቅና የባንኩን ገጽታ ለመገንባት እንዲቻል በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያላት፣ ታዋቂ ግለሰብና አርአያ በሆነች አርቲስት መቅደስ ፀጋዬ የባንኩን አገልግሎት ማስተዋወቅ አስፈላጊ መሆኑ የውል ስምምነቱ ሲደረግ ተገልጿል፡፡

በተለይም ባንኩ ፍትሃዊና ተደራሽ የሆነ የአገልግሎት አሰጣጥ በአዲስ መልክ ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ በጀመረበት ወቅት ባንኩን ማስተዋወቅ የባንኩን ገጽታ ለመገንባት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተነስቷል፡፡

በተጨማሪም ባንኩ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ተቋርጦ የነበረውን አገልግሎት በአዲስ መልክ ለመጀመር ዝግጅት በሚደረግበት ወቅት የባንኩን አገልግሎት በቋሚነት ማስተዋወቅ ለባንኩ መልካም አጋጣሚ ስለመሆኑም ተነስቷል፡፡  

የውል ስምምነቱ የተፈረመው በባንኩ ም/ፕሬዝዳንት ኮርፖሬት አገልግሎት እና አርቲስት መቅደስ ፀጋዬ መካከል ሲሆን፤ በሥነ ሥርዓቱ ላይ የባንኩ ፕሬዚዳንት ተገኝተዋል፡፡