የባንኩ ሰራተኞች ድምጻቸውን አሰሙ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሰራተኞች “ብሔራዊ ክብር በሕብር” በሚል በሀገራችን ላይ የሚደረግ ማንኛውንም ዓይነት የውጭ ጣልቃ ገብነትን በመቃወም ግንቦት 13 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00-11፡00 በዋናው መ/ቤት ፊት ለፊት በመገኘት ድምጻቸውን አሰምተዋል፡፡
በእለቱም፡-
- "የውጭ ኃይሎች እጃችሁን ከኢትዮጵያ ላይ እንድታነሱ እንጠይቃለን!"
- "ግድቡ የእኔ ነው!"
- :በሀገራችን ላይ የሚደረግ ማንኛውንም ዓይነት ጣልቃ ገብነትና ጫናን አንቀበልም!"
- "በሀገራችን የተጀመረውን ልማት እንደግፋለን!”
የሚሉ መፈክሮችን አሰምተዋል፡፡