የቋሚ ኮሚቴ አባላት ከባንኩ ጋር ውይይት አካሄዱ፤ ጉብኝት አደረጉ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የገቢ፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የ5ወር የሥራ አፈጻጸም ዙሪያ ከከፍተኛ ሥራ መሪዎች ጋር ግምገማዊ ውይይት ታህሳስ 24 ቀን 2012 ዓ.ም. አካሂደዋል፤ የመስክ ጉብኝትም አድርገዋል፡፡
ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ስለባንኩ የውስጥ አሠራር፣ ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር፣ የሪፎርምና መልካም አስተዳደር ሁኔታ፣ የፕሮጀክት አስተዳደር እና ከዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ገለጻ ተደርጓል፡፡
በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ባንኩ ትርፍ ማስመዝገቡም ተብራርቷል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው አባላት ለእርሻ ሥራ ተበድረው ስላልሰሩ ባለሃብቶች፣ ስለተበላሽ ብድር፣ ህዝቡ ስለ ባንኩ ያለውን አመለካከት ለመቀየር የህዝብ ግንኙነት ሥራ አስፈላጊነት እና በመሳሰሉት ዙሪያ ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡
በምላሹም ለእርሻ ሥራ ብድር ወስደው ባልመለሱ ሃለሃብቶች እና የተበላሸ ብድርን በሚመለከት እጃቸው ያለበት ሰዎች ለህግ እየቀረቡ እንደሆነ፣ በባንኩ የተገዙ ኢንቨስትመንቶች እየተሰበሰቡ እንደሚገኝ፣ ለገጽታ ግንባታ ሥራ በአምስት ዓመቱ የባንኩ ስትራቴጂክ ሪፎርም እቅድ ውስጥ መካተቱ ተብራርቷል፡፡
በመቀጠል የቋሚ ኮሚቴው አባላት የባንኩ ፕሮጀክቶች በሆኑት አይካ አዲስ ጨርቃ ጨርቅ እና ቢ.ኤም.ቲ. ኬብል ማምረቻ ፋብሪካዎች ጉብኝት አካሂደዋል፡፡
በመጨረሻም በቀረበው ገለጻ እና በመስክ ጉብኝቱ አባላቱ ስለ ባንኩ የነበራቸው ግምት መቀየሩን እና የተሻለ ግንዛቤ ማግኘታቸውንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡
Bid Announcement
The Development Bank of Ethiopia intends to sell the following projects which it has acquired due to defaulted loans in pursuant to proclamation No. 97/90 and 98/90.
Borrower’s/Guarantor’s Name |
Type and Address of the Property(project) |
Bid Type |
Level of Bid |
Bid Floor Price(Birr) |
Date and Time of Bid |
AYKA Addis Textile & Investment Group PLC |
An Integrated Textile Factory building, machineries, Equipment & furniture, vehicles, Auxiliary tools, various spare parts, Raw Materials/ inputs, work-in-progress, finished products /fabrics, and some other related items located at Sebeta town administration, Alemgena Wereda Kebele 08 on a plot area of 205,000m2
|
Closed Bid
|
Second |
1,956,601,072.76 |
January 14,2020 from 10:00 AM to 12:00 AM |
Else Addis Industrial Development PLC |
Textile and Ginning Factory building, machineries, Equipment and vehicles located at Adama Town, Kebele 05 on a plot area of 149,651 m2
|
Closed Bid
|
Second |
886,244,136.86 |
January 14,2020 from 10:00 AM to 12:00 AM |
Angel’s Cotton and Textile Production PLC |
Textile factory located in Oromia National Regional State Special Zone Surrounding Finfinne, Legetafo Legedadi Town, Kebele 02 with total area of 25,000 m2. The assets of the project to be disposed includes; buildings, machineries, Equipments, vehicles and others similar assets. |
Special Negotiation |
- |
258,819,423.22 |
January 14,2020 from 2:00 PM to 4:00 PM |
Omo Valley Farm Cooperation PLC |
Cotton Farm Project buildings, machineries, Equipment and vehicles located at South Omo Zone, Hammer Wereda, Kara koricho Kebele on a plot area of 10,000 ha
|
Special Negotiation |
- |
166,555,569.36 |
January 14,2020 from 2:00 PM to 4:00 PM |
Instructions፡
- Interested bidders can purchase a complete bidding document, in English, during the run of office hours from the Project Rehabilitation and Loan Recovery Directorate II of the Bank upon payment of non-refundable fee of Birr 100.00 (Birr One Hundred) in cash to Corporate Branch, and fill out the bid document with their name, the price they are going to offer and other information as required by the accompanying format. The complete Wax-sealed bid document should be received until January 14, 2020; 9:00AM through bid boxes placed in the Bank’s Head Office, second tower, ground floor starting from the third day of publication of this notice announcement.
- Bidders shall submit 10 % of the floor price only in CPO as an earnest.
- A winner shall pay the total acquisition price within 15(Fifteen) calendar days. Failure to pay within the specified time period shall be the cause for the loss of the earnest price and cancellation of the award.
- The Bid shall take place at the Head office of Development Bank of Ethiopia on the date and time specified in the table above.
- The winner is expected to pay 15% VAT (Fifteen Percent Value Added Tax), and all other legal and administrative fees and charges that are associated with the sale of the property.
- Since operations of AYKA Addis Textile & Investment Group PLC, Else Addis Industrial Development PLC and Angel’s Cotton and Textile production PLC are under DBE’s on-going scheme, on the top of winning price, the buyer is required to pay in cash/credit/the value of inventory items (item in transit, raw materials in stock, semi-finished products, items in progress, spare parts and finished products) which could be determined through valuation at the time of handing over of the property.
- The winner can apply for a loan facility for the unpaid balance as per the Bank’s Credit Policy and Procedure.
- Only the bidders or their legal representative will be allowed to attend the auction process.
- Interested and eligible bidders may obtain more information from the Development Bank of Ethiopia Project Rehabilitation and Loan Recovery Directorate II 2nd Tower 3rd Floor or through telephone 011-524-53-73. The Bank can arrange a pre-scheduled visit for interested bidders, up on prior notice to the Directorate.
- The Bank reserves the right to cancel the bid partially or fully.
THE DEVELOPMENT BANK OF ETHIOPIA
የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለሰጠው ብድር ማካካሻ የተረከባቸውን ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተመለከቱትን የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎች እና መካናይዝድ እርሻ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 98/90 በተሰጠው ስልጣን መሠረት በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል::
የተበዳሪው /የመያዣ ሰጪው/ ስም |
የሚሸጠው ንብረት(ኘሮጀክት) አድራሻና አይነት |
የጨረታ መነሻ ዋጋ (ብር) |
የጨረታ ሁኔታ |
የጨረታው ደረጃ |
የጨረታው ቀንና ሰዓት |
አይካ አዲስ ቴክስታይልና ኢንቨስትመንት ግሩፕ ኃ/የተ/የገል ማህበር |
በሰበታ ከተማ አስተዳደር አለም ገና ወረዳ ቀበሌ 08 በ205,000 ሜትር ካሬ ቦታ ላይ የተቋቋመ የተቀናጀ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ከነሙሉ ግንባታዎች፤ተሽከርካሪዎችን የምርት መሳሪያዎች፤ልዩ ልዩ መለዋወጫዎች ጥሬ ዕቃና ሙሉ በሙሉ ያለቀለት ምርት፤
|
1,956,601,072..76 |
ዝግ ጨረታ |
ሁለተኛ |
ጥር 5 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00-6፡00ሰዓት |
ኤልሲ አዲስ ኢንደስትሪያል ዲቨሎፕመንት ኃ/የተ/የግ/ማህበር |
በአዳማ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ 05 ክልል ውስጥ በ149,651 ሜትር ካሬ ቦታ ላይ የተቋቋመ የጨርቃ ጨርቅና የጥጥ መዳመጫ ፋብሪካ ከነሙሉ ግንባታዎች፤ የምርት መሳሪያዎች፤ ዕቃዎች እና ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ |
886,244,136.86 |
ዝግ ጨረታ |
ሁለተኛ |
ጥር 5 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00-6፡00ሰዓት |
ኤንጅልስ ከተን ኤንድ ቴክስታይል ፕሮደክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር |
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን፣ ለገጣፎ ለገዲዳ ከተማ ቀበሌ 02 ውስጥ በ25ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የተቋቋመ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ከነሙሉ ግንባታዎች፣ ማሽነሪዎች፣ ተሸከርካሪዎችና ሌሎች ተያያዥ ንብረቶችን ጨምሮ |
258,819,423.22 |
ልዩ ድርድር |
- |
ጥር 5 ቀን 2012 ከሰዓት በኋላ ከ8፡00-10፡00ሰዓት |
ኦሞ ቫሊ ፋርም ኮኦፐሬሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር |
በደቡብ ኦሞ ዞን፤ሐመር ወረዳ፤ ካራ ቆሪቾ ቀበሌ ውስጥ በ10,000 ሄክታር መሬት ላይ የተቋቋመ የጥጥ እርሻ ልማት ከነሙሉ ግንባታዎች፤ የምርት መሳሪያዎች፤ ዕቃዎች እና ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ |
166,555,569.36 |
ልዩ ድርድር |
- |
ጥር 5 ቀን 2012 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ከ8፡00-10፡00ሰዓት |
ማሳሰቢያ
- ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመግዛት ንብረቱን የሚገዙበትን ንብረት አይነት፤ የሚገዙበትን ዋጋ፣ ስምና አድራሻቸዉን በመጥቀስ ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን በማያያዝ በሰም በታሸገ ኢንቬሎኘ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ከሶስተኛዉ ቀን ጀምሮ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋናዉ መ/ቤት ሁለተኛ ታወር ምድር ቤት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀዉ ሣጥን እስከ ጥር 5 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ፤
- ተጫራቾች የሐራጁን መነሻ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ ክፍያ ማዘዣ /ሲ.ፒ.ኦ/ ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፤
- አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በ15 /በአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ካልከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሰንጠረዡ በተመለከተው ቀንና ሰዓት በባንኩ ዋናው መ/ቤት ይካሄዳል፤
- 15% የተጨማሪ እሴት ታክስና ሌሎች ገዢ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰነ ክፍያዎችን፣ የስም ማዛወሪያ ክፍያን ጨምሮ ገዢው ይከፍላል፤
- አይካ አዲስ ቴክስታይልና ኢንቨስትመንት ግሩፕ ኃ/የተ/የገል ማህበር፣ኤልሲ አዲስ ኢንደስትሪያል ዲቨሎፕመንት ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና ኤንጅልስ ከተን ኤንድ ቴክስታይል ፕሮደክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር የምርት ስራቸው ያልተቋረጠ በመሆኑ አሸናፊው ከግዢው ዋጋ በተጨማሪ በመጓጓዝ ወይም በክምችት ላይ ያሉ ግብአቶች /ጥሬ ዕቃዎች/ በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ያለቁ ምርቶችን በርክክብ ወቅት በሚደረስበት የትመና ዋጋ መሰረት በጥሬ ገንዘብ /በዱቤ/ ከፍሎ መውሰድ አለበት፤
- ባንኩ ለሽያጭ የቀረቡትን ንብረቶች የሚሸጠው ከተቻለ ሙሉ በሙሉ በጥሬ ገንዘብ ሲሆን አሸናፊው በባንኩ ብድር ፖሊሲ መሠረት አስፈላጊውን መስፈርቶች ካሟላና ፕሮጀክቱን የሚያስቀጥል ከሆነ ንብረቱን በከፊል ብድር ለመግዛት መጠየቅ ይችላል፡፡
- በጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ብቻ ናቸው፤
- ዝርዝር እና ተጨማሪ መረጃን በተመለከተ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋና መ/ቤት ታወር ሁለት ሦስተኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኘሮጀክት ማገገሚያና ብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት II በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 011--524-53-73 ደውሎ ማግኘት ይቻላል፡፡ ንብረቱን መጐብኘት የሚፈልጉም ካሉ ከዳይሬክቶሬቱ ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ መጐብኘት ይቻላል፤
- ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
ቦርዱ ከሠራተኞች ጋር ስብሰባ አካሄደ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የቦርድ ሥራ አመራር ከባንኩ ሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ጋር ጥቅምት 26 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም በኦሮሞ ባህል ማዕከል ስብሰባ አካሂዷል፡፡
የስብሰባው ዋና ዓላማ ከቦርዱ ጋር ትውውቅ ማድረግና ቦርዱ ያዘጋጀውን የ5 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ ማቅረብ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የቦርድ ሥራ አመራር ሰብሳቢ ዶ/ር ተገኘወርቅ ጌጡ በስብሰባው መክፈቻ ላይ ባንኩ ከ11ዐ ዓመት በላይ በሆነው ዕድሜው ለአገራችን ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ማበርከቱን ገልጸው፤ እንደቻይና፣ ብራዚል፣ ህንድ እና ፈረንሳይ አሁን ለደረሱበት የኢኮኖሚ ማማ መሠረታቸው የልማት ባንኮቻቸው መሆናቸውንም አክለዋል፡፡
ሆኖም ልማት ባንክ እንደሌሎች ዓለም አቀፍ ባንኮች ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲቀጥል ለማስቻል ቦርዱ የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ማዘጋጀቱን፤ በዕቅዱ የባንኩን ታሪካዊ ዳራ፣ አሁን ያለበት አቋም እና በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ የት መድረስ እንዳለበት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በመቀጠል በባንኩ የቦርድ አባልና የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው የ5 ዓመቱን ስትራቴጂክ ዕቅድ (እ.ኤ.አ. ከ2019-2023) አቅርበዋል፡፡
በስትራቴጂክ እቅዱ ባንኩ ከሌሎች ንግድ ባንኮች የተለየ ስለመሆኑ፤ ከዚህ ቀደም የነበረው ቢዝነስ ሞዴል ከአሠራር፣ ገቨርናንስ እና መዋቅር አኳያ ክፍተቶች የነበሩበት በመሆኑ አዲስ የቢዝነስ ሞዴል እንደሚያስፈልገው ተብራርቶ ቀርቧል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የባንኩን 27% የብድር ድርሻ የያዙትን የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ የቦርድ አባልና የኢትዮጵያ ጨርቃጨርቅ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ስለሺ ለማ አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለየሱስ በቀለ በበኩላቸው ቦርዱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ባንኩን በጥልቀት አጥንቶ ወደ ሥራ መግባቱን አድንቀዋል፡፡ ባለፈው በጀት ዓመት በብድር አሰባሰብ እና ክትትል ሥራ ላይ የነበሩ የሥራ ርብርብ ጥሩ እንደነበርም አክለዋል፡፡ ሆኖም ለብድር የተያዘ የመጠባበቂያ ወጪ /Provision/ አያያዝ ስርዓታችን መፈተሽ እንዳለበት እና በዓለም አቀፉ የሒሳብ ሪፖርት ሥርዓት /IFRS/ መሠረትም የምንሰራበት ይሆናል ብለዋል፡፡
በአጠቃላይ ቦርዱ ከያዘው ስትራቴጂክ ዕቅድና የለውጥ /ሪፎርም/ ሥራ ጋር በመሆን ባንኩ አሁን ካለበት ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ በማድረግ እናሻግረዋለን ብለዋል፡፡
በመቀጠል የቦርድ ሰብሳቢው መድረኩን ለተሰብሳቢዎች ክፍት አድርገው የተለያዩ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን ተቀብለዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል ቦርዱ ያዘጋጀው የ5 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ ጥሩ እንደሆነና የባንኩ ሠራተኞች እቅዱን ከግብ ለማድረስ ተግተው እንደሚሰሩ፣ ባንኩን በአግባቡ ሊጠቅሙ የሚችሉ ሆኖም ትኩረት ያልተደረገባቸው የሥራ ክፍሎች ስለመኖራቸው፣ ከኑሮ ውድነቱ አንጸር የደመወዝማ ሻሻያ፣ የቦነስ እና እርከን ጭማሪ ጉዳይ፣ የባንኩን ገጽታ ለመገንባት ለሚዲያ ጋዜጣዊ መግለጫ መስጠት ስለማስፈለጉ፣ ከምደባ፣ ዝውውርና እድገት አኳያ ክፍተቶች እንዳሉ፣ የባንኩ ችግሮች አብዛኛው ምንጭ ከውጭ አካላት ስለመሆኑና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
በመጨረሻም የቦርድ ሰብሳቢው የተነሱት ሀሳቦችና ጥያቄዎች ጥሩ እንደሆኑ እና በ5 ዓመቱ ስትራቴጂክ እቅዱ ውስጥ በዝርዝር እንደተቀመጡ፤ በሁሉም አቅጣጫ ባንኩን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ፣ ባንኩ ውጤታማ ከሆነ የሠራተኛ ጥያቄዎችን ማለትም ደመወዝ እና ሌሎች ጥቅማጥቅሞችን ከመመለስ ባሻገር በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አዎንታዊ ሚና ማሳረፍ እንደሚቻል፤ ስለሆነም ሁሉም የባንኩ ሥራ አመራርና ሠራተኛ ተባብሮ በመሥራት ስትራቴጂክ እቅዱን ከግብ ማድረስ እንደሚጠበቅበት አቅጣጫ ሰጥተው ስብሰባውን ቋጭተዋል፡፡
Page 26 of 30