የፀረ-ሙስና ቀን ተከበረ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሠራተኞችና ማኔጅመንት አባላት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ18ኛ ጊዜ፣ በሀገራችን ደረጃ ደግሞ ለ17ኛ ጊዜ የተከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን በባንኩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ “በሥነ ምግባር የታነፀ አመራር ከሙስና ለፀዳች ኢትዮጵያ!” በሚል መሪ ቃል ህዳር 30 ቀን 2014 ዓ.ም አክብረዋል፡፡
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የባንኩ ፕሬዝዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ የማኔጅመንት አባላት እና ሠራተኞች የተገኙ ሲሆን ለውይይት መነሻ የሚሆኑ ጽሑፎችም ለውይይት ቀርበዋል፡፡
በሥነ ሥርዓቱ መጀመሪያ ላይ የባንኩ ፕሬዝዳንት ክቡር ዮሐንስ አያሌው (ፒ.ኤች.ዲ) ባደረጉት ንግግር “በሥነ ምግባር የታነፀ አመራር ከሙስና ለፀዳች ኢትዮጵያ!” በሚል መሪ ቃል በዓሉን ስናከብር እኛም በሥነ ምግባራችን የታነፅን ሆነንና ለሌሎች አርአያ በመሆን ኃላፊነታችን በአግባቡ በመወጣት የባንካችንን ሥም እና ዝና ከፍ ልናደርግ ይገባል ያሉ ሲሆን አያይዘውም በቀጣይም የባንካችን ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በሥነምግባር የታነፁ እና ሙስናን የሚፀየፉ እና የሚታገሉ እንዲሆኑ ለማስቻል እንደ ብድር ሥራ ሁሉ የሥነ ምግባር ግንባታ ላይ በትኩረት የሚሰራ ሲሆን፣ በአጥፊዎች ላይ የሚወሰደው የእርምት እርምጃም የተጠናከረ ይሆናል ብለዋል፡፡
“የፍልስፍና ሚና በፀረ-ሙስና ጉዞ” በሚል ርዕስ በዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ እንዲሁም በባንኩ ውስጥ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ከመከላከል አንጻር የሥነ ምግባር ክፍሉ ያከናወናቸው ተግባራት እና ሙስናና ሥነ ምግባር የወቅቱ ቁልፍ ጉዳዮች በሚል ርዕስ በአቶ ወርቁ ፈቃደ የባንኩ የሥነ ምግባርና ቅሬታ መከታተያ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ለውይይት መነሻ የሚሆን ጽሑፍ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል፡፡
በመጨረሻም የባንኩ ፕሬዚዳንት ይህን በዓል ስናከብር ሙስናና ብልሹ አሰራር በሀገርና ተቋማት ላይ የሚያስከትለውን ተጽዕኖ በውል ተገንዝበን፣ ከመከላከል አንጻር የራሳችንን ድርሻ ወይም አስተዋጽዖ ተረድተን ኃላፊነታችንን መወጣት ይኖርብናል ያሉ ሲሆን እንደ ተቋም የኢትዮጵን ኢኮኖሚ የማሳደግ ኃላፊነት ተሰጥቶናል፡፡ ግልፅ የሆነ ራዕይና ተልዕኮም አስቀምጠናል፡፡ በዚህ ውስጥ የእኔ ድርሻ ምንድን ነው ብለን መጠየቅ ይኖርብናል፤ የባንኩ ሠራተኞችም በውሎው የተነሱ መልእክቶችን ከእለት ተእለት መደበኛ ሥራቸው ጋር በማዛመድ ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡
የባንኩ ሠራተኞች ደም ለገሱ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሠራተኞች “ደማችንን ለጀግኖቻችን በመለገስ አጋርነታችንን እናረጋግጣለን!” በሚል መሪ ቃል የሀገር ህልውናን ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮች እየተፋለሙ ለሚገኙ የመከላከያ ሠራዊትና በዘመቻው ላይ ለተሳተፉ ጀግኖች አለኝታነታቸውን ለማረጋገጥ ኅዳር 9 ቀን 2014 ዓ.ም በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት ደም ለግሰዋል፡፡
የደም ልገሳ ሥነ ሥርዓቱን በንግግር ያስጀመሩት የባንኩ ፕሬዚዳንት ክቡር ዮሐንስ አያሌው (ፒ.ኤች.ዲ) ሲሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሠራተኞች የሀገር ህልውናን የማስከበር ዘመቻ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ የወር ደመወዛቸውን ከማዋጣት አንስቶ የተለያዩ ድጋፎች በማድረግ ላይ መሆናቸውን ተናግረው፤ በደም ልገሳ የቀጠለው ድጋፍ ወደፊትም ባንኩም ሆነ ሠራተኞቹ የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ በማከልም ባንኩና ሠራተኞች ይህንን ሀገራዊ ጥሪ ለመመለስ ላሳዩት ተነሳሽነትና ፈቃደኝነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በደም ልገሳ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከ130 በላይ የባንኩ ሰራተኞች ደም ለመለገስ በፍቃደኝነት የተመዘገቡ ሲሆን ከ54 ዩኒት በላይ ደም መሰብሰቡን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የህልውና ዘመቻው ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ ባንኩ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የብር 106 ሚሊዮን ድጋፍ ማድረጉንና 12 የባንኩ ሠራተኞች ደግሞ ግንባር ድረስ መዝመታቸው ታውቋል፡፡
የደም ልገሳ መርኃ ግብሩ ላይ በመገኘት ደም የለገሱ የባንኩ ሠራተኞች በበኩላቸው ለሀገር ህልውና በተለያዩ ግንባሮች እየተዋደቀ ለሚገኘው ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ደም በመለገሳቸው ደስተኞች መሆናቸውን በመጠቆም ለወደፊቱም አጋርነታቸው ለማሳየት ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የእርሻ እና ምግብ ዓለምአቀፍ ንግድ ትርዒት በይፋ ተጀመረ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በፕላቲኒየም ደረጃ ስፖንሰር ያደረገው 13ኛው አዲስ ቻምበር የእርሻ እና ምግብ ዓለምአቀፍ ንግድ ትርዒት፣ እንዲሁም 4ኛው አዲስ ቻምበር ዓለምአቀፍ የማኑፋክቸሪንግ እና ቴክኖሎጂ ንግድ ትርዒት ህዳር 2 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኢግዚቢሽን ማዕከል በይፋ ተጀምሯል፡፡
በመክፈቻ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የባንኩ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም የአዲስ አበባ ንግድ እና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ባንኩም ቦታ በመረከብ ስለሚሰጣቸው የሊዝ እና ፕሮጀክት ብድር አገልግሎቶች መረጃ ሰጥቷል፤ የህትመትና ማስተዋወቂያ ቁሳቁሶችን በማሰራጨት በሰፊው አስተዋውቋል፡፡
የንግድ ትርዒቱ ከህዳር 02-06/2014 ዓ.ም እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡
Awareness Raising Workshop on ALMP Held
An awareness raising workshop held for successful suppliers who passes Agricultural Mechanization Leasing Project (ALMP) supplier due diligence requirement of the Bank at the Head Office on October 21, 2021.
The workshop was provided by expertise’s who came from GFA Consulting Group.
Opening the speech, A/Vice President, Small & Medium Enterprises Financing, Ato Abiot Daida said that the prime objective of this workshop is to create common understanding with stakeholders through awareness raising program. He said, and adding that this workshop will be taken as one of the requirements enables to implement Agricultural Mechanization Leasing Project with the Bank.
The successful suppliers, namely, Hagbes PLC, Moenco Ethiopia, Adeb Engineering & Trading PLC, ALT Agricultural Equipment Importers, Ethiopian Agricultural Business Corporation, Kaleb Service Farmers House PLC, Ultimate Motors PLC were in attendance in the workshop.
Finally, cooperation agreement was signed between the Bank and the successful suppliers.
Page 8 of 26