ሕጻናት ለልደታቸው በተቀመጠው ብር የቦንድ ግዥ ፈጸሙ
የአቶ በኃይሉ ዳንኤል ሶስት ህጻናት ልጆች እና ባለቤታቸው ልደታቸውን ለማክበር የተቀመጠላቸውን ብር ለቦንድ ግዥ አውለዋል፡፡ ግዥውን የፈጸሙት ሐምሌ 08 ቀን 2012 ዓ.ም በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋናው መ/ቤት በመገኘት ነው፡፡
በእለቱ የባንኩ ተ/ም/ፕሬዚዳንት ኮርፖሬት አገልግሎት አቶ ደሳለኝ ቦጋለ ይህ ተግባር ለሌሎች መሰል የነገ አገር ተረካቢ ህጻናት እና መላው ህብረተሰብ አርአያ የሚሆን ስለሆነ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል በማለት አበረታተዋል፡፡
በመቀጠል ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ኃይሉ አብርሐም በበኩላቸው መንግስት ህብረተሰቡን በማስተባበር ከመቼውም ጊዜ በተሻለ ግንባታውን እየፈጸመና የውሃ ሙሌቱንም እንደጀመረ ተናግረው ሌሎችም ይህን አርአያነት ያለው ተግባር በመከተል ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ቦንድ እንዲገዙ እና ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የሕጻናቱ አባት ሶስቱ ልጆቻቸው እና ባለቤታቸው ልደታቸውን ለማክበር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ብር አምስት ሺህ በድምሩ የብር 20 ሺህ ብር ቦንድ በራሳቸው ተነሳሽነት ገዝተዋል በማለት ገልጸዋል፡፡
በባንኩና በባንኩ ሠራተኛ ማህበር መካከል የሕብረት ስምምነት ፊርማ ሥነ ሥርዓት ተካሄደ
በኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና በባንኩ ሠራተኛ ማህበር መካከል ለ12ኛ ጊዜ የሕብረት ስምምነት ፊርማ ሥነ ሥርዓት ተካሄደ፡፡ የፊርማ ሥነ ሥርዓቱ የተካሄደው ሐምሌ 09 ቀን 2012 ዓ.ም በኢንተርኮንቲነንታል ሆቴል ነው፡፡
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለየሱስ በቀለ፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ የባንኩ ሠራተኛ ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉቀን አመነ እና ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የባንክና መድን ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ደስታ በርሔ ተገኝተዋል፡፡
የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለየሱስ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት ባንኩ ከሠራተኛ ማህበሩ ጋር በቅርበት ተሳስቦ እየሠራ እንደሚገኝ እና ይህ ተግባር ለወደፊቱም በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ በተያያዘም በህብረት ስምምነቱ ላይ ለተሳተፉት አካላት በሙሉ ምሥጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
የማህበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉቀን አመነ በበኩላቸው ማህበሩ የሠራተኛውን ጥቅማጥቅም ለማስከበር ከባንኩ ማኔጅመንት ጋር በውይይት እየሠራ የሚገኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ደስታ በርሔ በበኩላቸው የባንኩ ማኔጅመንት እና ሠራተኛ ማህበሩ በመነጋገርና በመወያየት ከአቻ ባንኮች ጋር ተመሳሳይ ጥቅማጥቅሞች እንዲከበሩ ለሚያደርጉት ጥረት በሙሉ ፌዴሬሽኑ አድናቆቱን ገልጾ ፌዴሬሽኑ ለወደፊቱ እገዛውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል፡፡
በህብረት ስምምነቱ ውስጥ አዲስ የገቡ እና የተሻሻሉ አንቀጾችና ንዑስ አንቀፆች ተካትተዋል፤ ከእነዚህ መካከል የሠራተኛ ቅጥር፣ ዝውውር፣ ደመወዝና ልዩ ማበረታቻ፣ የወሊድ ፈቃድ፣ የአባትነት ፈቃድ፣ ለሠራተኛ የሚሰጥ ብድር፣ ስለደረጃ ዕድገት፣ ትምህርትና ሥልጠና፣ የሕዝብ በዓላት፣ የትርፍ ሰዓት ሥራና ክፍያ፣ የቀን ውሎ አበል፣ የሐዘን ፈቃድ፣ ከሥራ ጋር ግንኙነት ስላለው በሽታና የአካል ጉዳት፣ በባንኩ የሚሸፈኑ የሕክምና ወጪዎች፣ የዲስፕሊን እርምጃ እንዲሁም ስለ ደንብ ልብስና የአደጋ መከላከያ ዘዴዎች ናቸው፡፡
ባንኩ ለሚዲያ አካላት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሰኔ 04 ቀን 2012 ዓ.ም. ለሚዲያ አካላት በኮቪድ-19 እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በኢንተርኮንቲነንታል ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለየሱስ በቀለ በአሁኑ ጊዜ በዓለምአቀፍም ሆነ በሀገራችን በተከሰተው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት በባንኩ ብድር የተቋቋሙ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ የራሱን አሉታዊ ተጽእኖ ማሳደሩን ገልጸው ባንኩም የራሱን የፕሮጀክት ማገገሚያ ስልቶችን በማዘጋጀት እና ጤናማ የሆኑ ፕሮጀክቶች በመለየት፣ በባንኩ ሥራ አስፈጻሚ እና ሥራ አመራር ቦርድ ታይተው ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግላቸው እና የልዩ ልዩ ማሻሻያዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ውሳኔዎች መተላለፋቸውን ተናግረዋል፡፡
በተቋም ደረጃም የባንኩን ሠራተኞች እና ደንበኞች ከወረርሽኙ ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መሠራታቸውን፣ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች (ሳኒታይዘር እና አልኮል) መከፋፈላቸውን፤ በሥራ ቦታ አካላዊ ርቀት ተጠብቆ እንዲሠራ መደረጉን፣ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎች መታደላቸውን እና በሥራ መግቢያና መውጫ ሰዓት የትራንስፖርት አገልግሎት መመቻቸቱን ገልጸዋል፡፡
ኮቪድ-19 የሚያደርሰውን ወረርሽኝ ለመከላከል እንዲቻል በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተቋቋመው የኮቪድ-19 ግብረ ኃይል እንዲሁ የአምስት ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን የባንኩ ፕሬዚዳንት ተናግረዋል፡፡
የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት (MFIs) እና የኅብረት ሥራ ማኅበራት ባጋጠማቸው የገንዘብ እጥረት እና የእነሱ ተጠቃሚ ለሆኑ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ደንበኞቻቸው በአነስተኛ ወለድ የብድር አቅርቦት እንዲስተናገዱ መደረጉን አቶ ኃይለየሱስ ጨምረው አብራርተዋል፡፡
በመጨረሻም ከእርሻ ብድሮች ጋር በተያያዘ እንዲሁም የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በባንኩ ገቢ ላይ ስላስከተለው ጉዳት እና በቀጣይ ምን ለመሥራት እንደታሰበ ከሚዲያ ባለሙያዎች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
DBE Holds its 3rd Quarter Meeting via Video Conference
Development Bank of Ethiopia /DBE/ held the first ever video conference its Third Quarter Management Meeting in using Zoom platform on May 15 & 16, 2020 aims to prevent the wide-spreading of Corona Virus (COVID-19).
During the two days meeting, performance report of the Bank in all districts and at the corporate level was presented and important discussion was held over by management members of the Bank.
The report covered credit operations, the change related activities, financial, HR and other function’s performance of the Bank for the third quarter and nine months, problems encountered, corrective measures taken, strengths and weaknesses assessed and the way forward.
While chairing the meeting, President of the Bank, Ato Haileyesus Bekele said from this online meeting and discussion, significant inputs will be gathered for the next year plan preparation.
According to the report presented, the credit operations performance of the Bank for this quarter is better than that of the previous year same period. Overall, the Bank registers satisfactory level performance by approving birr 2.3 billion, disbursement of birr 2.2 billion and collection of birr 2.16 billion both in project and lease financing.
The Bank also sold Grand Renaissance Bond amounted to birr 133.7 million during the quarter.
Finally, Ato Haileyesus Bekele said despite many challenges facing such as COVID-19 pandemic, we should work hard in smarter way to achieve set targets by reducing of NPLs, increasing the volume of bond sales, and loan collection.
Page 24 of 31