ባንኩ የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር አስተባባሪነት “አንድ ጫማ ለአንድ ተማሪ” በሚል መሪ ቃል ጥቅምት 16 ቀን 2012 ዓ.ም ለአዲስ አበባ ተማሪዎች በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ በመገኘት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

 

የገንዘብ ድጋፉን በሸራተን ሆቴል በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ በአካል በመገኘት ለአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ያስረከቡት የባንኩ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ አያሌው (ፒ.ኤች.ዲ) ናቸው፡፡