በባንኩ ሲሰጥ የነበረው ሀገር አቀፍ ስልጠና ተጠናቀቀ

ከሰኔ 02 እስከ 06 ቀን 2013 ዓ.ም አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች በሚገኙ 12 የስልጠና ማዕከላት ለአምስት ተከታታይ ቀናት በባንኩ ሲሰጥ የቆየው ሀገር አቀፍ የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ስልጠና ሰኔ 06 ቀን 2013 ዓ.ም ተጠናቋል፡፡

ስልጠናው ከመጠናቀቁ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ሰኔ 05 ቀን 2013 ዓ.ም የባንኩ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ አያሌው (ፒ.ኤች.ዲ) ከአዲስ አበባና ከየስልጠና ማዕከላቱ ከሰልጣኞች ለተነሱ ጥያቄዎች በተለይም በሊዝ ፋይናንሲንግ የማሽነሪ ብድር ፖሊሲ እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ሰልጣኞች ስለ ስልጠናው ገንቢ አስተያየታቸውን ለግሰዋል፡፡ እንደ ሰልጣኞች አስተያየት የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠናው ከጠበቁት በላይ ሆኖ እንዳገኙት እና ወደፊትም ከባንኩ ጋር በሚኖራቸው የሥራ ግንኙነት በእውቀት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን እንዳስቻላቸው ገልጸው ባንኩ ይህን መሰል ስልጠና በማመቻቸቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡