በባንኩ የፀረ ሙስና ቀን ተከበረ
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ17ኛ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ16ተኛ ጊዜ “የትውልድ የስነ ምግባር ግንባታን በጠንካራ ዲሲፕሊን በመምራት ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን በመታገል የብልፅግና ጉዟችንን እናፋጥናለን!” በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፉን የፀረ ሙስና ቀን በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ተከብሯል፡፡
በባንኩ የስነ ምግባርና ቅሬታ መከታተያ ቢሮ አስተባባሪነት ህዳር 25 ቀን 2013 ዓ.ም በተዘጋጀው በዚህ ስነ ስርዓት ላይ የባንኩ ም/ፕሬዚዳንት ኮርፖሬት አገልግሎት አቶ ሰፊዓለም ሊበን ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም የባንኩ ሰራተኞች ሙስናን በመከላከል ረገድ በታማኝነት ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል፡፡
በተለይም ከዚህ ቀደም የተከሰቱ ግድፈቶችን በመፈተሸና በማጥናት ለውስጣዊና ውጫዊ ጫናዎች መከሰት በር የሚከፍቱ አሰራሮችን ለመዝጋት እንዲቻል ግልፅ የሆነ አሰራሮችንና መመሪያዎችን በማዘጋጀት የባንኩን መልካም ስምና ዝናውን ለማደስ የሚያስችሉ ስራዎችን ለመስራት ከሁሉም ሰራተኛ ቁርጠኝነት እንደሚጠበቅ አውስተው ቀኑን ስናከብር ከራሳችን ህይወት በመጀመር ሁላችንም የተጣለብንን ኃላፊነት በታማኝነት መወጣት መቻል ራሳችንንም ሆነ ባንካችንን ከአደጋ መጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በስነ ስርዓቱ ላይ በዳኛቸው አሰፋ /ፒ.ኤች.ዲ/ ሙስና ከፖለቲካ ከህግና ከሞራል አንጻር ያለው አንድምታን በሚመለከት እንዲሁም በአቶ ወርቁ ፈቃደ የሥነ ምግባርና ቅሬታ መከታተያ ቢሮ ኃላፊ ለውይይት መነሻ የሚሆኑ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
የባንኩ ሰራተኞች “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርኃ ግብር ላይ ተሳተፉ
በሀገር አቀፍ ደረጃ ህዳር 08 ቀን 2013 ዓ.ም፣ ከረፋዱ 5፡30 ላይ “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ!” በሚል መሪ ቃል በተከበረው ስነ ስርዓት ላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሰራተኞች ተሳተፉ፡፡
ለመከላከያ ሰራዊታችን ያለንን ክብር በመግለፅ ከጎኑ መቆማችንን ለማረጋገጥ በተዘጋጀው በዚህ ስነ ስርዓት ላይ የባንኩ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ አያሌው /ፒ.ኤች.ዲ/፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ የሥራ መሪዎችና ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አገልግሎቱን የበለጠ ተደራሽ ለማድረግ መጠን ሰፊ የሪፎርም ስራዎችን በመተግበር ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ባንኩ የኮር ባንኪንግ ሲስተሙን የበለጠ ለማዘመን እና ተግባራዊ ለማድረግ ይረዳው ዘንድ ከህዳር 9 ቀን እስከ ህዳር 11 ባሉት ቀናት መደበኛ አገልግሎቱን የማይሰጥ መሆኑን እየገለፅን ከላይ በተጠቀሱት ቀናት ገንዘብ ለማስገባት የሚፈልጉ ደንበኞች በተቻለ መጠን እስከ ህዳር 9 ቀን 2013 ገቢ ክፍያዎችን እንዲፈፅሙ እያሳሰብን ከህዳር 10 እስከ ህዳር 12 ቀን 2013 ዓ.ም ባሉት ቀናት ገቢ ክፍያዎችን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ አቢሲኒያ ባንክ እና ወጋገን ባንክ ቅርንጫፎች መፈፀም እንደምትችሉ ለክቡራን ደንበኞቻችን በአክብሮት ያሳውቃል፡፡
የኢትየጵያ ልማት ባንክ፤ የልማት አጋርዎ!
Auction Announcement
Development Bank of Ethiopia intends to sell the collateralized properties shown in the table below, repossessed from a defaulted borrower –Seka Agro Processing plc pursuant to the power vested to it under Proclamation No. 97/98 and 98/98.
Name of the borrower |
Property location |
Type of property |
Plot size |
Auction floor Price (in Birr) |
Level of auction |
Date &time auction |
Seka Agro Processing plc |
South Nations Nationalities &Peoples Regional State, Benji Shiko Zone,Gura-ferda Woreda, Guja kebele |
Mango plant farm and rice processing factory with building, machinery, equipment & furniture, vehicles, auxiliary tools, various spare parts, and some other related items |
2,714 hectares of farm area and 4.61 Hectares of Rice processing factory |
199,376,460.19 (One Hundred Ninety Nine Million Three Hundred Seventy Six Thousand Four Hundred Sixty Birr and Nineteen Cents) |
Second |
Dec.16,2020 From 10:00 am to 12:00 am |
Instructions፡
- Bidders shall submit 25 % (twenty five percent) of the floor price only in CPO as an earnest.
- The winner shall pay the total auction price within 15(Fifteen) calendar days. Failure to pay within the specified time period shall be the cause for the loss of the earnest price and cancellation of the award. Besides, the winner shall also be held responsible for the shortfall that may occur during the re-auctioning of the property.
- CPO of non-winner bidders will be returned back.
- Only the borrower or his legal representative, bidders or their legal representative and concerned government organs will be allowed to attend the auction process that takes place at the farm site located at Benji Shiko zone,Guraferda Woreda, Guja kebele, on the date & time specified in the table above.
- The winner shall pay 15% Value Added Tax, and all other legal and administrative fees and charges that are associated with the sale of the property.
- As the farm is in operation, the winner, on top of the winning price, is also required to pay in cash/partial credit the value of items that might have been purchased after the publication of this announcement, the value of which shall be determined at the time of handing over the property. If an agreement cannot be reached, the Bank reserves the right to take over the items.
- Some of the Properties Such like vehicles, Farm machineries, etc. have been procured under duty free privileges. Thus, the winner needs to either have matching customs duty exemption privilege or shall pay the outstanding duties.
- The winner can apply for a loan facility for the unpaid balance as per the Bank’s Credit Policy and Procedure. However, a winner who is interested to purchase the farm on credit basis is required to submit, to the bank, documents that confirm he/she/it, under his/he/its name and/or a company in which he/she/it holds 10%(Ten percent) or above share/s, is clear from any statutory or other liabilities, including unsettled payment claims.
- Interested and eligible Participants may obtain more information from the Development Bank of Ethiopia Project Rehabilitation and Loan Recovery Directorate-II 2nd Tower 3rd Floor or through telephone 011-524-53-73 or can be accessed on the website of the Bank. www.dbe.com.et. The Bank can arrange a pre-scheduled visit for interested Participants.
- The Bank reserves the right to cancel the auction partially or fully.
THE DEVELOPMENT BANK OF ETHIOPIA
Page 21 of 31