Development Bank of Ethiopia
Toggle Navigation
  • Home
  • Contact Us
  • About
    • Mission, Vision and Value
    • History
    • Bank Mandates
    • Board Memebers
    • Excutive Members
    • Organizational Stracture
  • Services
    • Banking Services
    • Bond Issuing
    • Loan Requirments
    • Rural Electrification
    • Priority Sectors
    • Export Credit Gurantee
    • International Banking
    • Project Financing
    • RUFIP
  • Publication
    • Annual Report
      • 2021
      • 2020
      • 2019
      • 2018
      • 2017
      • 2016
      • 2015
      • 2014
      • 2013
    • Brochure
    • Zena Lemat Bank
    • Bond Flayer
    • Dev't News Letter
      • News Letter 1
      • News Letter 2
      • News Letter 3
      • News Letter 4
      • News Letter 5
  • Notice
    • Bid
    • Foreclosure
    • Vacancy
    • Rate
  • Address
    • Head Office
    • Directorate/Office
    • Districts and Branch Offices
  • FAQ
  • banner1.jpg
  • banner3.jpg
  • banner4.jpg
  • Development-partner2.jpg
  • Mining.jpg
Previous Next Play Pause
  • Credit ServiceCredit Service
  • RUFIPRUFIP
  • BondBond
  • IBSIBS
  • ECGECG

ባንኩ ስፖንሰር ያደረገው ከወለድ ነጻ የባንክ እና የኢንሹራንስ አገልግሎት መድረክ ተካሄደ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በዋና አጋርነት ስፖንሰር በማድረግ የተሳተፈበት ከወለድ ነጻ የባንክ እና የኢንሹራንስ አገልግሎት ላይ ያተኮረ መድረክ መጋቢት 7 ቀን 2014 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ተካሂዷል፡፡

 

 

በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ የአካውንቲንግ እና ኦዲቲንግ ቦርድ ዳይሬክተር ጄኔራል፣ የግል ባንክ እና ኢንሹራንስ ተወካዎች፣ ባለድርሻ አካላት እና አማካሪ ድርጅቶች ተገኝተዋል፡፡

ባንኩን በመወከል መድረኩ ላይ የተገኙት ም/ፕሬዚዳንት- ኮርፖሬት አገልግሎት አቶ ሰፊዓለም ሊበን መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ በመልእክታቸው የኢትዮዽያ ልማት ባንክ የሸሪአ መርሆዎችን የተከተለ ከወለድ ነጻ የሆነ የትላልቅ ፕሮጀክትና የሊዝ የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ተገቢውን ጥናት አስጠንቶ አገልግሎቱን ባስቀመጣቸው ስትራቴጂዎች በቅርቡ እውን ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

 

ባንኩ በሌሎች ባንኮች ሊሸፈኑ የማይችሉ የፋይናንስ አገልግሎቶችን በማቅረብና የሀገሪቱን የማክሮ ኢኮኖሚ ክፍተት በመሙላት በሀገራዊ እድገት ላይ የራሱን ሚና በመጫወት እንደሚገኝ በመግለጽ አገልግሎቱን ከሚሹ ሁሉም ደንበኞቹ ጋር በጋራ ለመስራት ባለው ጠንካራ ፍላጎት የተነሳ የረጅም ጊዜ ብድር ወስደው በልማት ስራ ላይ በማዋል ራሳቸውንና ሀገራቸውን እንዲያሳድጉ  ም/ፕሬዚዳንቱ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በቀጣይነትም ባንኩ ሀገራዊ እድገት ላይ አስተዋጽኦ ያላቸውን የግንዛቤ መፍጠሪያ መሰል መድረኮችን ለመደገፍ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አክለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሰራተኞች የሴቶች ቀን /March 8/ አከበሩ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሰራተኞች በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ46ተኛ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ111ኛ ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን /March 8/ መጋቢት 29 ቀን 2014ዓ.ም በባንኩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አክብረዋል፡፡

“እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” እና “የስርዓተ ፆታ እኩልነት ለዘላቂ ልማት” በሚሉ መሪቃሎች በተከበረው በዓል ላይ የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች፣ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽ የሴቶች ጉዳይ መምሪያ ሃላፊ ወ/ሮ ራሄል አየለ፣ የኢትዮጵያ ፋይናንስ ተቋማት ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ደስታ በርሄ እንዲሁም የባንኩ ሴት አመራሮችና ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የባንኩን ፕሬዝዳንት በመወከል የተገኙት የኮርፖሬት አገልግሎት ም/ፕ አቶ ሰፊዓለም ሊበን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን፤ በመልእክታቸውም በማህበረሰባችን ውስጥ ተደራራቢ ሃላፊነትን በመወጣት ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማድረግ ትልቁን ቁጥር የሚይዙት ሴቶች መሆናቸውን ገልፀው እንደ ተቋምም እንደ ማህበረሰብም ሴቶችን ማገዝና መደገፍ ውጤታማ ስራ ለመስራት መሰረት እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ አክለውም ሴቶችን ለማብቃት እና የባንኩን የሴት አመራሮች ቁጥር ለመጨመር እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡  

የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽ የሴቶች ጉዳይ መምሪያ ሃላፊ ወ/ሮ ራሄል አየለ በበኩላቸው ባስተላለፉት መልእክት ሴቶች እድሉ ከተሰጣቸውና ራሳቸውን እንዲያበቁ እገዛ ቢደረግላቸው ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት የሚያስችል እምቅ ሃይልና ችሎታ ባለቤት ናቸው ያሉ ሲሆን፤ ባንኩ ሴቶችን ወደ አመራር ቦታ ለማምጣት ትኩረት ሰጥቶ አንዲሰራ ጠይቀዋል፡፡ አያይዘውም “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚለው መርህ መሰረት ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በተለይም ወንድ ሰራተኞች የሴቶችን ጥቃል ለመከላከል ዘብ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ ሀገራችን በገጠማት የህልውና ማስከበር ጦርነት ወቅት ሃገራቸውን እና ወገናቸውን ከጥቃት ለመታደግ የህይወት መሰዋዕትነት ለመክፈል በመቁረጥ በፍቃደኝነት ለዘመቱ የባንኩ ሰራተኞች የእውቅና አሰጣጥ ስነስርዓት ተካሂዷል፡፡

 

 

ባንኩ ከማዕድን ሚኒስቴር ጋር ውይይት አደረገ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከማዕድን ሚኒስቴር ጋር በትብብር መሥራት በሚችልባቸው አስቻይ ሁኔታዎች ዙሪያ ጥር 26 ቀን 2014 ዓ.ም በባንኩ ዋናው መሥሪያ ቤት ውይይት አድርጓል፡፡

በውይይቱ ላይ የባንኩ ፕሬዚዳንት የተከበሩ ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው /ፒ.ኤች.ዲ/ እና ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ ከማዕድን ሚኒስቴር በኩል ደግሞ የተከበሩ አቶ ታከለ ኡማ እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

የባንኩ ፕሬዚዳንት የተከበሩ ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው (ፒ.ኤች.ዲ) ስለባንኩ ፖሊሲዎችና አሰራሮች፣ እንዲሁም ብድር ስለሚሰጥባቸው መስፈርቶች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ከብድር ሥራ ጎን ለጎን በስልጠና እና በትብብር /partnership/ መሥራት ስለሚቻልባቸው አስቻይ ሁኔታዎች ገለጻ አድርገዋል፡፡

የማዕድን ሚኒስትሩ በተደረገላቸው ገለጻ አመስግነው በቀጣይ በማዕድን ልማት ዘርፍ ከባንኩ ጋር በትብብር በመሥራት በአገር ኢኮኖሚ እድገት ላይ ለውጥ ለማምጣት እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

 

 

ባንኩ ከዲያስፖራ ማኅበረሰብ ጋር ውይይት አካሄደ

ባንኩ የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ጥሪን ተከትለው ወደ ሀገራቸው ከገቡ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን /ዲያስፖራ ማኅበረሰብ/ ጋር ጥር 27 ቀን 2014 ዓ.ም በባንኩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሂዷል፡፡

በውይይቱ ላይ የባንኩ ፕሬዚዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ የዲያስፖራ ማኅበረሰብ ማህበር ተወካዮች፣ የማህበሩ አባል የሆኑ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን /የዲያስፖራ ማኅበረሰብ/ ተገኝተዋል፡፡

በውይይቱ ወቅት የባንኩ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው /ፒ.ኤች.ዲ/ ስለባንኩ የቀድሞ አሠራር፣ አሁንናዊ ሁኔታ እና ለወደፊቱ ሊሰሩ ስለታቀዱ ሥራዎች፣ እንዲሁም የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድን መሠረት በማድረግ ስለተጀመሩ የለውጥ ሂደቶች አጠር ያለ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ በጋምቤላ ክልል የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ተረክቦ ማስቀጠል ለሚችል ዳያስፖራ አስፈላጊውን ሂደት ተከትሎ መሥራት የሚችልበት ሁኔታ የተመቻቸ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በመቀጠል ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ከባንኩ ስለሚፈልጉት እገዛ እና ተያያዥ ጉዳዮች ያሏቸውን ጥያቄዎች እንዲያነሱ መድረኩን ክፍት አድርገዋል፡፡

በውይይቱ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎች እና አስተያየቶችን  ያነሱ ሲሆን በዋናነትም የባንኩ የብድር አሰጣጥ ሂደትን ቀልጣፋ አለመሆን፣ የውጭ ምንዛሪ አሰጣጥ፣ የወለድ ምጣኔ እና የብድር አመላለስ፣ እንዲሁም  የእፎይታ ጊዜን በተመለከተ ግልጽ የሆነ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው የጠየቁ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ከባንኩ ፕሬዝዳንት በተሰጠው ምላሽ የባንኩ ወለድ ምጣኔ 11.5 መሆኑን ገልጸው ይህም በሃገራችን ካሉ የንግድ ባንኮች አንፃር ሲታይ አነስተኛ መሆኑ ለዳያስፖራው ጠቀሜታ እንዳለው ገልፀዋል፡፡ የእፎይታ ጊዜን በተመለከተም እንደፕሮጀክቱ ዓይነት የሚታይ ሆኖ ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት እንደሚሆን ምላሽ ተሰጥቶበታል፡፡

ተሳታፊዎቹ ባንኩ ይህን መድረክ በማዘጋጀቱ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን ባንኩን ባላቸው የእውቀት እና ቴክኖሎጂ ሙያ ዘርፎች የበኩላቸውን እገዛ ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

 

  1. በጉለሌ ክ/ከ በባንኩ የገንዘብ ድጋፍ የተገነቡ የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶች ተመረቁ
  2. በባንኩ የገንዘብ ድጋፍ የተገነቡ የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶች ተመረቁ

Page 6 of 26

  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • ...
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • ...

Lease Finance

  • Brochure
  • Requirements
  • Feasibility study contents above 10 million
  • Business plan content below 10 million

Credit Service

  • Guide to Access DBE's Loans
  • Loan Requirments and their purpose
  • Priority Areas
  • Revised Credit Policy Feb 2018

External Fund and Credit Management Directorate

  • Press Release on Disbursement of Interest Rate Subsidy
  • Social Assessment For The Women Entrepreneurship Development Project Additional Financing (WEDP AF)
  • Environmental And Social Management Framework (ESMF) Update - Women Entrepreneurship Development Project Additional Financing
  • ESMF Final RUFIP III
  • SME Audit Report 2019/20
  • WEDP-Financial statement 2019/20
  • DBE-ENREP-Audit 2019-20.pdf
  • SME Audited Financial Statement 2018/19
  • MDRE & EEP Audited Financial Statement 2018/19
  • WEDP Audited Financial Statement 2018/19
  • ELECTRICITY NETWORK REINFORCEMENT PROJECT audit report for june 30 2018
  • WEDP (Field visit annex Audit report)
  • Audit Report Financial Statement 2018
  • Auditors' Report on WEDEP Grant
  • RUFIP News II
  • RUFIP News Updates
  • Documents
  • Electricity Network Reinforcement
  • Independent Auditor's Report
  • Audit Report 2018
  • DBE-WEDP Audit Report 2021
  • DBE-SMEFP Audit Report 2021
  • DBE-ENREP Audit Report 2021/22

DBE advert

  • DBE advertDBE advert

DBE Location

  • DBE LocationDBE Location

Branch Location

  • Branch LocationBranch Location
feed-image My Blog

Back to Top

© 2023 Development Bank of Ethiopia