Development Bank of Ethiopia
Toggle Navigation
  • Home
  • Contact Us
  • About
    • Mission, Vision and Value
    • History
    • Bank Mandates
    • Board Memebers
    • Excutive Members
    • Organizational Stracture
  • Services
    • Banking Services
    • Bond Issuing
    • Loan Requirments
    • Rural Electrification
    • Priority Sectors
    • Export Credit Gurantee
    • International Banking
    • Project Financing
    • RUFIP
  • Publication
    • Annual Report
      • 2021
      • 2020
      • 2019
      • 2018
      • 2017
      • 2016
      • 2015
      • 2014
      • 2013
    • Brochure
    • Zena Lemat Bank
    • Bond Flayer
    • Dev't News Letter
      • News Letter 1
      • News Letter 2
      • News Letter 3
      • News Letter 4
      • News Letter 5
  • Notice
    • Bid
    • Foreclosure
    • Vacancy
    • Rate
  • Address
    • Head Office
    • Directorate/Office
    • Districts and Branch Offices
  • FAQ
  • banner1.jpg
  • banner3.jpg
  • banner4.jpg
  • Development-partner2.jpg
  • Mining.jpg
Previous Next Play Pause
  • Credit ServiceCredit Service
  • RUFIPRUFIP
  • BondBond
  • IBSIBS
  • ECGECG

 

ባንኩ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞችን ፋይናንስ ለማድረግ ያለመ ውይይት ከመንግስትና የግሉ ዘርፍ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር መጋቢት 01 ቀን 2013 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ አካሂዷል፡፡

በውይይቱ ላይ የባንኩ ፕሬዚዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶችና ዲስትሪክት ስራ አስኪያጆች እንዲሁም የፌዴራል እና ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የአምራች ዘርፍ፣ የግል ባንኮች እና አነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት የሥራ መሪዎች ተገኝተዋል፡፡

ስብሰባውን በንግግር የከፈቱት የፌዴራል አነስተኛ መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ማስፋፊያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አስፋው አበበ እንዳሉት ለሀገር በቀል ኢኮኖሚ ትልቅ ተስፋ የተጣለበትን አነስተኛ መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ፋይናንሲንግ ዙሪያ ለመነጋገር በተዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ ፋይናንስ ለኢንዱስትሪው ዘርፍ ልማት የደም ስር መሆኑንና ያለ ፋይናንስ የኢንዱስትሪውን ልማት ከፍ ማድረግ እንደማይቻል ጠቅሰዋል፡፡

የውይይት መድረኩ መዘጋጀት ዋነኛ ዓላማ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፎችን ፋይናንስ በማድረግ ሂደት ያጋጠሙ ችግሮችን ከአሠራርና ከአፈጻጸም አኳያ በመገምገም ችግሮቻቸውን ማስተካከል በሚቻልበት ዙሪያ እና ተቋርጦ የነበረውን የማሽነሪ ሊዝ ፋይናንሲንግ ውጤታማ በሆነ መንገድ ፋይናንስ ለማድረግ በዓለም ባንክ ለዘርፉ የተደረገውን የ8.6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ በአግባቡ ለመጠቀም የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ለማምጣት መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡

በአምራች ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ላይ ተሰማርተው የፋይናንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የመስሪያ ቦታ እና የገበያ ትስስር ክፍተት ያለባቸውን ኢንተርፕራይዞች ችግር ለማቃለል የተገኘውን ሀብት በአግባቡ ለመጠቀም ተቀናጅቶ መስራት ወሳኝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዮሐንስ አያሌው /ፒ.ኤች.ዲ/ በበኩላቸው በተለያዩ ምክንያቶች ተቋርጦ የቆየውን የካፒታል ዕቃ ኪራይ አገልግሎት በአዲስ መልክ ለመጀመር ቀደም ሲል ዘርፋን ሲያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን በመቅረፍ ብድር ወደመስጠት ለመሄድ ደንበኞች መብትና ግዴታቸውን እንዲያውቁና ስለሚሰሩት ሥራ በቂ ግንዛቤና ራዕይ ሊኖራቸው ስለሚገባ ባንኩ በሰባት ማዕከላት ስልጠና ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡

ባንኩ ከስልጠና በኋላ ለሚሰጠው የማሽነሪ ሊዝ ፋይናንስ፣ የሥራ ማስኬጃ ብድር (Working capital) እና የፕሮጀክት ብድር ባለድርሻ አካላት ከባንኩ ጎን በመሆን አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡ በተለይም ቀደም ሲል ሲስተዋል የነበረውን የቅንጅት ችግር በመቅረፍ በተናበበና በትብብር መንፈስ አምራች ዘርፉን መደገፍ እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የተገኙት ባለድርሻ አካላት በሰጡት አስተያየት በአጭር ጊዜ ውስጥ ባንኩ ተግባራዊ እያደረገ ያለውን የሪፎርም ሥራ በማድነቅ ባንኩ የሚሰራቸውን ሥራዎች በግንባር ቀደምትነት ለመደገፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡   

የአነስተኛ መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ለማስፋፋት የዛሬ አራት ዓመት መንግስት በሰጠው አቅጣጫ ከጥቃቅንና አነስተኛ ወደ አነስተኛና መካከለኛ የተሸጋገሩ (the missing middle) ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ ችግር ለመፍታት በርካታ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ሰፊ ውይይት ተደርጎ የተጀመረ ሥርዓት መሆኑ ይታወሳል፡፡ 

 

ባንኩ ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀንንአ ከበረ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን /March 8/ የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ.ም በባንኩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ያከበሩ ሲሆን፤ የባንኩን ፕሬዚዳንት ጨምሮ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እና የባንኩ ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡

በሥነ ስርዓቱ የባንኩ መሰረታዊ ሰራተኞች ማህበር የሴቶች ተወካይ ወ/ሮ ኦሪት አበበ በባንኩ ውስጥ ሴቶች ያላቸው የአመራርነት ድርሻ አነስተኛ በመሆኑ ለወደፊቱ ሴቶችን የማብቃትና ወደ ኃላፊነት የማምጣት ተግባር ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ተግባር መሆኑን አንስተዋል፡፡

የባንኩ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ አያሌው /ፒ.ኤች.ዲ/ በበኩላቸው በባንኩ ውስጥ የሴቶች ቁጥር በአመራር ቦታ አነስተኛ መሆኑን እና በባንኩ ውስጥ እየተከናወነ ባለው የሪፎርም ስራ ላይ በአንጽዖት እንደሚታይ ቃል ገብተዋል፡፡

በመጨረሻም የባንኩን ሴቶች በመወከል ንግግር ያደረጉት ወ/ሮ አልማዝ ጥላሁን እንዳሉት የሴቶች ቀን ሲከበር የበዓሉን ማክበር ብቻ ሳይሆን ሴቶች ላይ የሚደርሱ አሉታዊ ተጽዕኖዎችና ጥቃቶችን በመከላከል ሴቶችን ለተሻለ ውጤት በማብቃት ጭምር መሆን እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡

 

የባንኩ BSC ወርክሾፕ ላይ የማጠቃለያ መርኃ ግብር ተካሄደ

ባንኩ ከየካቲት 08-17/2013 ዓ.ም ሲያካሂድ የነበረውን አዲስ የውጤት ተኮር ምዘና ስርዓት ስልጠና /BSC/ የማጠቃለያ መርኃ ግብር የካቲት 26 ቀን 2013 ዓ.ም በባንኩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አካሂዷል፡፡

 በማጠቃለያ መርኃ ግብሩ ላይ የባንኩ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ም/ፕሬዚዳንቶች ዳይሬክተሮችና የቡድን ሥራ አስኪያጆች የተገኙ ሲሆን፤ የዲስትሪክት እና  ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆች በዙም /zoom meeting/ ስብሰባውን ተሳትፈዋል፡፡

ስብሰባውን በንግግር የከፈቱት የባንኩ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ አያሌው /ፒ.ኤች.ዲ/ ሲሆኑ እንደርሳቸው ገለጻ ይህ የውጤት ተኮር ምዘና /BSC/ ወርክሾፕ ባንኩ ለጀመረው የሪፎርም ስራ አንዱ አጋዥ መሳሪያ ነው ብለዋል፡፡

ባንካችንን ደረጃውን የጠበቀ ባንክ /world class/ ለማድረግ የሚያስችል ቢዝነስ ሞዴል እየተዘጋጀ መሆኑን እንዲሁም ተግባራዊ እየተደረገ ባለው ባንኩ የጀመረውን ለውጥ ውጤታማ እንዲሆን ለማድረግ ሁሉም የስራ መሪና ሰራተኛ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ እንደሚገባም ጨምረው ተናግረዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ ቀሪ ጊዜ ውስጥ የተጀመረውን የሪፎርም ሥራ በሚፈለገው ጥራትና ፍጥነት ለማከናወን በውጤት ተኮር የምዘና ሥርዓት /BSC/ መታገዝ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በተለይም ባንኩ የብድር አሰባሰብ ማሳደግ፣ የተበላሸ የብድር ምጣኔ መቀነስ፣ የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት እና ጥራት ያለው የብድር አሰጣጥ ተግባራዊ ማድረግ ላይ በውጤት ተኮር የምዘና ሥርዓት ታግዞ መስራት ለውጤት እንደሚያበቃ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ መጨረሻም ሆነ በቀጣዮቹ ተከታታይ ዓመታት የባንኩን የተበላሸ የብድር ምጣኔ ለመቀነስ እንዲቻል የተጀመረውን ሪፎርም ስራ ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የባንኩ የውጤት ተኮር ምዘና (BSC) ከባንኩ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ተቆርሶ እስከ ሠራተኛ ድረስ የሚወረድበት አሠራር ለመዘርጋት በከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲከለስ መደረጉን አብራርተዋል፡፡

 

የተከለሰውን የውጤት ተኮር ምዘና በአጭር ጊዜ ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ ይቻል ዘንድም በሶስት ማዕከላት ማለትም በባንኩ ዋና መ/ቤት፣ በባህርዳርና ሀዋሳ ስልጠናዎች ሲሰጡ እንደነበር ተናግረዋል፡፡

 

ለሪፎርሙ መሳካትም 7 ስትራቴጂክ ምሶሶዎች፣ 26 ስትራቴጂክ ዓላማዎች እና ቁልፍ የአፈፃፀም አመልካቾች ሠራተኛ ድረስ በማውረድ ባንኩ ውስጥ ግልጽነት እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ለማድረግ ታስቦ እየተሰራበት እንደሚገኝ አክለው ገልጸዋል፡፡

 

 

 

የባንኩ የማሻሻያ ስራዎች ቀጣይነታቸው እንዲረጋገጥ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ የገንዘብ ሚኒስቴር ገለጸ

  • የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ባለፉት ስድስት ወራት ያከናወናቸው ዋና ዋና የማሻሻያ ስራዎች የባንኩን ትርፋማነት ለማሳደግ እንዳስቻለ ተገልጿል፡፡

 

በገንዘብ ሚኒስትሩ በክቡር አቶ አህመድ ሽዴ በተመራ ግምገማ ላይ እንደተገለጸው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ትርፋማነቱ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በብር 304.16 ሚሊዮን ብልጫ ማለትም በ150 በመቶ ከፍ ያለ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

አቶ አህመድ ሽዴ የባንኩ ትርፋማነት የተገኘው ተለያዩ የለውጥ ስራዎች በመተግበራቸው እንደሆነ በግምገማው ወቅት አብራርተዋል:: በተለይም ባንኩ የነበረውን ብድር የማስተዳደርና የመቆጣጠር አቅም ማሳደጉ ለዚህ ውጤት እንዳበቃው ተናግረዋል፡፡

 

በተጨማሪም የኢትዮጵያ የልማት ባንክ በስድስት ወር ውስጥ የህዳሴ ግድብ ቁጠባን በተመለከተ ብር 500 ሚሊየን ለመፈፀም አቅዶ ብር 883.47 ሚሊየን ለመሰበብሰብ መቻሉ የሚበረታታ መሆኑም በግምገማው ተመልክቷል፡፡ በተለይም ኢትዮጵያዊያን በራሳቸው አቅም እየገነቡት ያለው የህዳሴ ግድብ ወቅቱን ጠብቆ ማጠናቀቅ እንዲቻል ባንኩ ጥረቱን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክን የማሻሻያ ስራዎች ውጤታማነታቸውን ቀጣይ ለማድረግ ባንኩ በአዳዲስ እና በቴክኖሎጂ የታገዙ የአሰራር ስርዓቶችን ማጎልበት፣ የባንኩን የውጭ ምንዛሪ አቅም ማሳደግ እና የባንኩን አማራጭ የሀብት ምንጭ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ቀዳሚ ትኩረት የሚሹ መሆናቸውን አቶ አህመድ ሽዴ አስረድተው፤ ባንኩን በዘላቂነት ከሀብት ጥገኝነት ለማውጣት የማሻሻያ ስራዎች በወጣላቸው መርሀ ግብር መሰረት መተግበር እንደሚኖርባቸውም ማሳሰባቸው  ታውቋል፡፡

 

  1. በባንኩ ስትራቴጂክ ሪፎርም እቅድ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ
  2. ባንኩ በተለያዩ ፖሊሲዎችና መመሪያዎች ዙሪያ ወርክሾፕ አካሄደ

Page 14 of 26

  • 9
  • ...
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • ...
  • 16
  • 17
  • 18

Lease Finance

  • Brochure
  • Requirements
  • Feasibility study contents above 10 million
  • Business plan content below 10 million

Credit Service

  • Guide to Access DBE's Loans
  • Loan Requirments and their purpose
  • Priority Areas
  • Revised Credit Policy Feb 2018

External Fund and Credit Management Directorate

  • Press Release on Disbursement of Interest Rate Subsidy
  • Social Assessment For The Women Entrepreneurship Development Project Additional Financing (WEDP AF)
  • Environmental And Social Management Framework (ESMF) Update - Women Entrepreneurship Development Project Additional Financing
  • ESMF Final RUFIP III
  • SME Audit Report 2019/20
  • WEDP-Financial statement 2019/20
  • DBE-ENREP-Audit 2019-20.pdf
  • SME Audited Financial Statement 2018/19
  • MDRE & EEP Audited Financial Statement 2018/19
  • WEDP Audited Financial Statement 2018/19
  • ELECTRICITY NETWORK REINFORCEMENT PROJECT audit report for june 30 2018
  • WEDP (Field visit annex Audit report)
  • Audit Report Financial Statement 2018
  • Auditors' Report on WEDEP Grant
  • RUFIP News II
  • RUFIP News Updates
  • Documents
  • Electricity Network Reinforcement
  • Independent Auditor's Report
  • Audit Report 2018
  • DBE-WEDP Audit Report 2021
  • DBE-SMEFP Audit Report 2021
  • DBE-ENREP Audit Report 2021/22

DBE advert

  • DBE advertDBE advert

DBE Location

  • DBE LocationDBE Location

Branch Location

  • Branch LocationBranch Location
feed-image My Blog

Back to Top

© 2023 Development Bank of Ethiopia